የትውልድ አሻራ

 የትውልድ አሻራ
 ayeleradio@gmail.com 
የዓባይ  ወንዝ  በመጽሐፍ  ቅዱስ  ኦሪት  ዘፍጥረት  ምዕራፍ 2 10 - 15 እንደተጠቀሰው ከኤድን ወንዝ ወጥቶ ገነትን ያጠጣል፡፡ ከኤድን የወጣው ይህ ወንዝ በአራት በመከፈል ፊሶን፣ ግዮን፣ ጤግ ሮስ እና ኤፍራጥስ በመባል ይጠራል፡፡ ከነዚህ መካከል  ግዮን ተብ  የሚጠራው ወንዝ “የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል፡፡” ተብሎ ተገልፃል፡፡ ይህ ወንዝ የዓባይ ወንዝ እንደሆነ ይነገራል፡፡

የዓባይ ወንዝ በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ ግሽ ዓባይ ከተባለ የግሽ ተራራ ይነሳል፡፡ ወንዙ ከምንጩ ከፈለቀ በኋላ ጅምር ጅረት፣ ብሎም ወንዝ ሲሆን ግልገል ዓባይ በመባል ይጠራል፡፡

የተወሰኑ ኪሎሜትሮችን ተጉዞ በዚሁ በምእራብ ጎጃም ዞን ደቡብ አቸፈር ወረዳን ከሜጫ ወረዳ ከሚያገናኘው ድልድይ አካባቢ ሲደርስ ወተት ዓባይ (ቢኮሎ አባይወይም ትንሹ አዓባይ የሚል ስያሜ ተሰጥቶት ትዝታውን ጥሎ ጉዞውን ወደ አማራ ክልል ርእሰ መዲና ባህርዳር ጣና ሃይቅ በመግባት ጉልበቱን አጠናክሮ ጉዞውን ወደ ደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በማዞር በቀድሞው አጠራር ጎጃምና ጎንደርን በሚያገናኘውና ባህርዳር ከተማን በምስራቅ እንደቀለበት እየከበበ ጥንታዊ ድልድይ ስር አዲስ ታሪክ ጽፎ ያልፋል፡፡ ጉዞ ብቻ ሳይሆን ታሪክ መስራት ማይታክተው ዓባይ ከጣና ሃይቅ ተለይቶ 30 ኪሎ ሜትር እንደተጓዘ ጢስ ዓባይ የተባለውንና እጅግ ሳቢውብ እና የቱሪስት መስህብ የሆነውን አስደናቂውን ጢስ ዓባይ ፏፏቴ ይፈጥራል፡፡ “በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ” እንዲሉ ፏፏቴው ከቱሪስት መስህብነቱ ባለፈ 64 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃል አመንጭቶ በአዲስ መልክ ዝቅ ያለው ረዥሙ ጎርጅ ውስጥ ራሱን ደብቆ እንደቀትር እባብ እየተጥመዘመዘ ይቀጥላል፡፡ ጎዞ ይጀምራል፡፡ ለአካባቢው አርሶ አደሮች የመስኖ አገልግሎት ይውላል፡፡ እንዲህ እንዲህ እያለ ወሎና ጎጃምን እያካለለ በሚሌኒየሙ ድልድይ አማካኝነት ጎጃምን ከሸዋ አገናኝቶ 1 ሺህ ኪሎ ሜትር ያህል ተጉዞ የትውልድ ሀገሩን ለቆ ጎረቤት አገር ሱዳን ከመግባቱ በፊት እንደ ንፉግ ልጅ ከተደበቀበት ወጥቶና ደረቱን ሜዳ ላይ አስጥቶ እንቁልልጭ እያለ ይወጣል፡፡

የዓባይ ወንዝ ሀገራችን ካሏት የገፀ-ምድር የውሃ ሃብቶች 46 በመቶ ያህሉን ይሸፍናል፡፡ የተፋሰሱ 25 በመቶ የሀገራችንን የቆዳ ስፋት በመሸፈን 20 በመቶ የህዝባችን የኑሮ ህልውና፣ 35 በመቶ የውሃ ሃይል ምንጭና 40 በመቶ የመስኖ ልማት መሰረት ሊሆን የሚችል ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው ተፋሰስ ነው፡፡ የዓባይ ተፋሰስ አስራ አንድ ሀገራትን የሚያካልል ቢሆንም ለዘመናት በተፋሰሱ ሀገራት መካከል ፍትሐዊ የውሃ አጠቃቀም ባለመኖሩ ሀገራችን ኢትዮጵያ የጥቅሙ ተቋዳሽ መሆን ሳትችል ቆይታለች፡፡

ዛሬ ግን  በመንግስትና በህዝቦቿ ቁርጠኛ ውሳኔ ታሪክ ተቀይሮ ሃገራችን ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሃብቷን በመጠቀም ልማቷን ማረጋገጥ የሞት ሽረት ጉዳይ ከመሆን ባለፈ ፍፁም መብቷ መሆኑን ለዜጎቿ በማስረፅ ፊቷን ወደ ፀጋዎቿ አዙራ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ከጀመረች ውላ አድራለች፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራችን በዓባይ ወንዝ ላይ የምትገነባው የህዳሴ ግድብም የዚህ ሉዓላዊ መብቷ አንዱ ማሳያ ነው፡፡ ከቀድሞ ጀምሮ ኢትዮጵያ በወሰን ተሻጋሪ ወንዞቿ ላይ ያላት አቋም በመርህ ላይ የተመሰረተ እና የሁሉንም የተፋሰሱ አገራት በተለይም ግርጌ አገሮችን መብት የጠበቀ  ከመሆኑ ባሻገር በፍትሃዊነት የምንጠቀምበት የጋራ ሃብታችን እንዲሆን በተለያዩ መንገዶች ስታስረዳ ቆይታለች፡፡

ኢትዮጵያ እየገነባችው ያለው የህዳሴ ግድብ የተያያዘችውን ድህነትን ድል የመንሳት፣ ልማትን የማረጋገጥ እና የዜጎችን ፍላጎት የማሟላት ራዕይ ከማሳካት አንፃር ብቻ ሳይሆን የግድቡ መገንባት ለምስራቅ አፍሪካ አገሮች ከሚሰጠው ጥቅም ባለፈ ሁለንተናዊ ፋይዳውም ከፍተኛ ነው፡፡

ካለፉት 10 ዓመታት ወዲህ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የልማትና የዴሞክራሲ ግንባታ ስራዎች ከተመዘገበው ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ጋር ተያይዞ ሃገራችን ኢትዮጵያ ከዘመናት የኋልዮሽ ጉዞ ተላቃ በአዲስ የህዳሴ ጎዳና ጉዞ መጀመሯን ያሳያል፡፡ ይህ የህዳሴ ጉዞም የምልዓተ ህዝቡን ይሁንታ ያገኘና የህዝብ ንቅናቄ የተፈጠረበት በመሆኑ የሃገሪቱ ህዳሴ እውን እንደሚሆን የሚያመላክት ነው፡፡ በተለይም በራሳችን የፋይናንስ አቅም ልንገነባው የተነሳነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዓባይ ጉዳይ የበዪ ተመልካች መሆኑ ሲቆጨው የኖረውን ህዝብ ጥያቄ የመለሰ ከመሆኑም በላይ የተስፋ ቆራጭነትና የጠባቂነት አመለካከትን በመስበር የይቻላል መንፈስን በማላበሱ በሃገሪቱ የልማት ታሪክ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሰፊ ልማታዊ መነቃቃት እንዲፈጠር አግዟል፡፡

በመሆኑም የግድቡ መጀመር ይፋ ከሆነበት ከመጋቢት 24/2003 . አንስቶ መላ ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ ያለምንም የዕድሜ፣ የፆታ፣ የሃይማኖትና የገቢ ልዩነት በቦንድ ግዥና በልገሳ በታሪክ ሲወሳ የሚኖር የፋይናንስ አስተዋፅኦ አበርክተዋል፡፡ እያበረከቱም ይገኛሉ፡፡ በአቅም ማነስ ምክንያት ይሄን ማድረግ ያልቻሉ የህብረተሰብ ክፍሎች በዚህ ታሪካዊ ፕሮጀክት ላይ አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ለማድረግና ተጨማሪ አስተዋፅኦ የሚያበረክቱበትን እድል ለማመቻቸት 8100 የአጭር የሞባይልና የልዩ ሎተሪ ገቢ ማስገኛ ፕሮግራም በመነደፉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን በማሳተፍ የዚህ ታሪካዊ ክንውን አካል እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል፡፡

ከዚህ ባለፈ የሃገራችን አርሶ አደሮችም የግድቡን ዕድሜ ለማራዘም ከደለል ለመከላከልና ለመጠበቅ ባለፉት 6 ዓመታት የፈፀሙትና አሁንም በመፈጸም ላይ ያሉት የአካባቢ ጥበቃና የተፋሰስ ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ይህም የጉልበት አስተዋፅኦ ከአስራ ስምንት ቢሊዮን በላይ የሚቆጠር ገንዘብ ግምት ያለው ከመሆኑም በላይ እየተከናወነ ያለው ታላቅ ስራ ሃገራችን አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት ለቀየሰችው ስትራቴጂ ስኬት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡ ይህን ሁሉ ስኬታማ ተግባር ለማከናወን የተቻለው መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለግድቡ ግንባታ እውን መሆን እንደ “አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ አፍ ተናጋሪ” ሆኖ በየዘርፉ የሚጠበቅበትን ሁሉ እየፈፀመ በመሆኑ ነው፡፡ 

ለአብነት የአማራ ክልልን እንቅስቃሴ ብቻ ወስደን ብናይ ከጥር 2004 እስከ ጥር 30/2009 . ድረስ፡-

ከመንግስት ሰራተኞች 462 ሚሊዮን 630 ሺህ 344 ብር፣ ከባለሃብቱና ከንግዱ ማህበረሰብ 85 ሚሊዮን 018 ሺህ 865 ብር፣ ከአርሶ አደሩ 211 ሚሊዮን 662 ሺህ 391 ብር፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች 258 ሚሊዮን 330 ሺህ 629 ብር እና ከተለያዩ አካላት (በልገሳ የተሰጠ) 7 ሚሊዮን 215 ሺህ 327 ብር በድምሩ 1 ቢሊዮን 024 ሚሊዮን 857 ሺህ 552 ብር መሰብሰብ ተችሏል፡፡
እንዳጋመስነው እንጨርሰዋለን!!



ተጨማሪ እውነታዎች

  



የዓባይ  ወንዝ  በመጽሐፍ  ቅዱስ  ኦሪት  ዘፍጥረት  ምዕራፍ 2 10 - 15 እንደተጠቀሰው ከኤድን ወንዝ ወጥቶ ገነትን ያጠጣል፡፡ ከኤድን የወጣው ይህ ወንዝ በአራት በመከፈል ፊሶን፣ ግዮን፣ ጤግ ሮስ እና ኤፍራጥስ በመባል ይጠራል፡፡ ከነዚህ መካከል  ግዮን ተብ  የሚጠራው ወንዝ “የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል፡፡” ተብሎ ተገልፃል፡፡ ይህ ወንዝ የዓባይ ወንዝ እንደሆነ ይነገራል፡፡

የዓባይ ወንዝ በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ ግሽ ዓባይ ከተባለ የግሽ ተራራ ይነሳል፡፡ ወንዙ ከምንጩ ከፈለቀ በኋላ ጅምር ጅረት፣ ብሎም ወንዝ ሲሆን ግልገል ዓባይ በመባል ይጠራል፡፡

የተወሰኑ ኪሎሜትሮችን ተጉዞ በዚሁ በምእራብ ጎጃም ዞን ደቡብ አቸፈር ወረዳን ከሜጫ ወረዳ ከሚያገናኘው ድልድይ አካባቢ ሲደርስ ወተት ዓባይ (ቢኮሎ አባይወይም ትንሹ አዓባይ የሚል ስያሜ ተሰጥቶት ትዝታውን ጥሎ ጉዞውን ወደ አማራ ክልል ርእሰ መዲና ባህርዳር ጣና ሃይቅ በመግባት ጉልበቱን አጠናክሮ ጉዞውን ወደ ደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በማዞር በቀድሞው አጠራር ጎጃምና ጎንደርን በሚያገናኘውና ባህርዳር ከተማን በምስራቅ እንደቀለበት እየከበበ ጥንታዊ ድልድይ ስር አዲስ ታሪክ ጽፎ ያልፋል፡፡ ጉዞ ብቻ ሳይሆን ታሪክ መስራት ማይታክተው ዓባይ ከጣና ሃይቅ ተለይቶ 30 ኪሎ ሜትር እንደተጓዘ ጢስ ዓባይ የተባለውንና እጅግ ሳቢውብ እና የቱሪስት መስህብ የሆነውን አስደናቂውን ጢስ ዓባይ ፏፏቴ ይፈጥራል፡፡ “በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ” እንዲሉ ፏፏቴው ከቱሪስት መስህብነቱ ባለፈ 64 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃል አመንጭቶ በአዲስ መልክ ዝቅ ያለው ረዥሙ ጎርጅ ውስጥ ራሱን ደብቆ እንደቀትር እባብ እየተጥመዘመዘ ይቀጥላል፡፡ ጎዞ ይጀምራል፡፡ ለአካባቢው አርሶ አደሮች የመስኖ አገልግሎት ይውላል፡፡ እንዲህ እንዲህ እያለ ወሎና ጎጃምን እያካለለ በሚሌኒየሙ ድልድይ አማካኝነት ጎጃምን ከሸዋ አገናኝቶ 1 ሺህ ኪሎ ሜትር ያህል ተጉዞ የትውልድ ሀገሩን ለቆ ጎረቤት አገር ሱዳን ከመግባቱ በፊት እንደ ንፉግ ልጅ ከተደበቀበት ወጥቶና ደረቱን ሜዳ ላይ አስጥቶ እንቁልልጭ እያለ ይወጣል፡፡

የዓባይ ወንዝ ሀገራችን ካሏት የገፀ-ምድር የውሃ ሃብቶች 46 በመቶ ያህሉን ይሸፍናል፡፡ የተፋሰሱ 25 በመቶ የሀገራችንን የቆዳ ስፋት በመሸፈን 20 በመቶ የህዝባችን የኑሮ ህልውና፣ 35 በመቶ የውሃ ሃይል ምንጭና 40 በመቶ የመስኖ ልማት መሰረት ሊሆን የሚችል ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያለው ተፋሰስ ነው፡፡ የዓባይ ተፋሰስ አስራ አንድ ሀገራትን የሚያካልል ቢሆንም ለዘመናት በተፋሰሱ ሀገራት መካከል ፍትሐዊ የውሃ አጠቃቀም ባለመኖሩ ሀገራችን ኢትዮጵያ የጥቅሙ ተቋዳሽ መሆን ሳትችል ቆይታለች፡፡

ዛሬ ግን  በመንግስትና በህዝቦቿ ቁርጠኛ ውሳኔ ታሪክ ተቀይሮ ሃገራችን ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሃብቷን በመጠቀም ልማቷን ማረጋገጥ የሞት ሽረት ጉዳይ ከመሆን ባለፈ ፍፁም መብቷ መሆኑን ለዜጎቿ በማስረፅ ፊቷን ወደ ፀጋዎቿ አዙራ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ከጀመረች ውላ አድራለች፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራችን በዓባይ ወንዝ ላይ የምትገነባው የህዳሴ ግድብም የዚህ ሉዓላዊ መብቷ አንዱ ማሳያ ነው፡፡ ከቀድሞ ጀምሮ ኢትዮጵያ በወሰን ተሻጋሪ ወንዞቿ ላይ ያላት አቋም በመርህ ላይ የተመሰረተ እና የሁሉንም የተፋሰሱ አገራት በተለይም ግርጌ አገሮችን መብት የጠበቀ  ከመሆኑ ባሻገር በፍትሃዊነት የምንጠቀምበት የጋራ ሃብታችን እንዲሆን በተለያዩ መንገዶች ስታስረዳ ቆይታለች፡፡

ኢትዮጵያ እየገነባችው ያለው የህዳሴ ግድብ የተያያዘችውን ድህነትን ድል የመንሳት፣ ልማትን የማረጋገጥ እና የዜጎችን ፍላጎት የማሟላት ራዕይ ከማሳካት አንፃር ብቻ ሳይሆን የግድቡ መገንባት ለምስራቅ አፍሪካ አገሮች ከሚሰጠው ጥቅም ባለፈ ሁለንተናዊ ፋይዳውም ከፍተኛ ነው፡፡

ካለፉት 10 ዓመታት ወዲህ በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የልማትና የዴሞክራሲ ግንባታ ስራዎች ከተመዘገበው ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ጋር ተያይዞ ሃገራችን ኢትዮጵያ ከዘመናት የኋልዮሽ ጉዞ ተላቃ በአዲስ የህዳሴ ጎዳና ጉዞ መጀመሯን ያሳያል፡፡ ይህ የህዳሴ ጉዞም የምልዓተ ህዝቡን ይሁንታ ያገኘና የህዝብ ንቅናቄ የተፈጠረበት በመሆኑ የሃገሪቱ ህዳሴ እውን እንደሚሆን የሚያመላክት ነው፡፡ በተለይም በራሳችን የፋይናንስ አቅም ልንገነባው የተነሳነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በዓባይ ጉዳይ የበዪ ተመልካች መሆኑ ሲቆጨው የኖረውን ህዝብ ጥያቄ የመለሰ ከመሆኑም በላይ የተስፋ ቆራጭነትና የጠባቂነት አመለካከትን በመስበር የይቻላል መንፈስን በማላበሱ በሃገሪቱ የልማት ታሪክ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሰፊ ልማታዊ መነቃቃት እንዲፈጠር አግዟል፡፡

በመሆኑም የግድቡ መጀመር ይፋ ከሆነበት ከመጋቢት 24/2003 . አንስቶ መላ ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ ያለምንም የዕድሜ፣ የፆታ፣ የሃይማኖትና የገቢ ልዩነት በቦንድ ግዥና በልገሳ በታሪክ ሲወሳ የሚኖር የፋይናንስ አስተዋፅኦ አበርክተዋል፡፡ እያበረከቱም ይገኛሉ፡፡ በአቅም ማነስ ምክንያት ይሄን ማድረግ ያልቻሉ የህብረተሰብ ክፍሎች በዚህ ታሪካዊ ፕሮጀክት ላይ አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ለማድረግና ተጨማሪ አስተዋፅኦ የሚያበረክቱበትን እድል ለማመቻቸት 8100 የአጭር የሞባይልና የልዩ ሎተሪ ገቢ ማስገኛ ፕሮግራም በመነደፉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን በማሳተፍ የዚህ ታሪካዊ ክንውን አካል እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል፡፡

ከዚህ ባለፈ የሃገራችን አርሶ አደሮችም የግድቡን ዕድሜ ለማራዘም ከደለል ለመከላከልና ለመጠበቅ ባለፉት 6 ዓመታት የፈፀሙትና አሁንም በመፈጸም ላይ ያሉት የአካባቢ ጥበቃና የተፋሰስ ልማት ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ይህም የጉልበት አስተዋፅኦ ከአስራ ስምንት ቢሊዮን በላይ የሚቆጠር ገንዘብ ግምት ያለው ከመሆኑም በላይ እየተከናወነ ያለው ታላቅ ስራ ሃገራችን አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት ለቀየሰችው ስትራቴጂ ስኬት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡ ይህን ሁሉ ስኬታማ ተግባር ለማከናወን የተቻለው መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለግድቡ ግንባታ እውን መሆን እንደ “አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ አፍ ተናጋሪ” ሆኖ በየዘርፉ የሚጠበቅበትን ሁሉ እየፈፀመ በመሆኑ ነው፡፡ 

ለአብነት የአማራ ክልልን እንቅስቃሴ ብቻ ወስደን ብናይ ከጥር 2004 እስከ ጥር 30/2009 . ድረስ፡-

ከመንግስት ሰራተኞች 462 ሚሊዮን 630 ሺህ 344 ብር፣ ከባለሃብቱና ከንግዱ ማህበረሰብ 85 ሚሊዮን 018 ሺህ 865 ብር፣ ከአርሶ አደሩ 211 ሚሊዮን 662 ሺህ 391 ብር፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች 258 ሚሊዮን 330 ሺህ 62ብር እና ከተለያዩ አካላት (በልገሳ የተሰጠ) 7 ሚሊዮን 215 ሺህ 327 ብር በድምሩ 1 ቢሊዮን 024 ሚሊዮን 857 ሺህ 552 ብር መሰብሰብ ተችሏል፡፡
እንዳጋመስነው እንጨርሰዋለን!!



ተጨማሪ እውነታዎች



 
ተ.ቁ
የፕሮጀክቱ ስም
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ
1
የግድቡ ባለቤት
የኢትዮጵያ ህዝቦችና መንግስት
2
የግድቡ ፈንድ
የኢትዮጵያ ህዝቦችና መንግስት
3
ግድቡ የሚገኝበት ቦታ
በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ጉባ ወረዳ
4
ግንባታው የተጀመረበት ቀን
መጋቢት 24/2003 ዓ.ም እ.ኢ.አ
5
የግድቡ ስራ ዓይነት
RCC (ኮንክሪት ሙሌት)
6
የግድቡ ተቋራጭ (ሲቪል ስራዎች)
ሳሊኒ ኢምፕሬጂሎ
7
የኤሌክትሮ መካኒካል ስራዎች
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ብ/ብ/ኢ/ኮርፖሬሽን
8
የግድቡ ኃይል የማመንጨት አቅም
ሺህ 450 ሜጋ ዋት
9
የዋናው ግድብ ከፍታ
145 ሜትር
10
የዋናው ግድብ ርዝመት
1.8 ኪሎ ሜትር
11
የዋናው ግድብ ውፍረት
ከታች 120 ሜትር፣ ከላይ 8 ሜትር
12
የኮርቻ (ሳድል) ግድቡ ከፍታ
50 ሜትር
13
የኮርቻ (ሳድል)ግድቡ ርዝመት
5.2 ኪሎ ሜትር
14
የኃይል ማከፋፈያው ጣቢያ አቅም
500 ኪሎ ቮልት
15
የኃይል ማስተላለፊያው አቅም
500 ኪሎ ቮልት
16
የግድቡ ውሃ የመያዝ አቅም
74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር
17
ግድቡ የሚይዘው ቦታ ስፋት
ሺ 680 ስኬዌር ሜትር
18
የግድቡ ውሃ የሚተኛበት ቦታ ርዝመት
246 ኪሎ ሜትር
19
በግድቡ ያሉ ሰራተኞች ብዛት
10 ሺህ 672
20
የውጭ ሃገር ዜጎች ብዛት
317
21
በስራ ላይ ያሉ ማሽነሪዎች
ሺህ 300
22
ግድቡ በዓመት ሊያስገኝ የሚችለው ገቢ
ከ 2 ቢሊዮን ዶላር በላይ
23
ግድቡን የጎበኙ ሰዎች (በአማራ ክልል ብቻ)
170 ሺህ
24
ግድቡ የደረሰበት ደረጃ
ከ56 በመቶ በላይ






































































































Comments